ሐረር

ከWikipedia

ሀረር በግምብ የተከበችው ጀጎል
ሀረር በግምብ የተከበችው ጀጎል

ሃረርአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ በአምስት መቶ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተማ ናት። በዘመኑ የአስተዳደር መዋቅር የሃረሪ ክልል ዋና ከተማ ናት። በ1,885 ሜትር ከፍታ ላይ፣ የወይና ደጋ የአይር ጠባይ በተላበሰ ቦታ ላይ አርፋለች። በምድር መጋጠሚያ ውቅር 9°19′ ሰሜን ኬክሮስ እና 42°7′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ናት። በ1987 ዓመተ ምህረቱ የህዝብ ቆጠራ መሰረት ሃረር 76,378 ሕዝብ ይኖርባታል።

ሃረር ለዘመናት ከፍተኛ የንግድ ማዕከል ሆና ስትኖር ከመሃል አገር፣ ከአፍሪካ ቀንድ እና ከአረብ አገራት ጋር በንግድ መንገዶች ስትገናኝ ከቀሪው አለም ጋር ደግሞ በቀይ ባህር ወደቦች አማካኝነት ትገናኝ ነበር።

የሃረር ጀጎል ግንብ ከ1998 ጀምሮ በዩኔስኮ የአለም ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ይገኛል። በእስልምና ሃይማኖት "4ኛዋ የተቀደሰች ቦታ" ተብላም ስትታወቅ 82 መስጊዶች፤ አንዳንዶቹ ከ10ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበሩ፤ እንዲሁም 102 የቀብር ቦታዎች አሉዋት።

[ለማስተካከል] መጠቆሚያዎች


ኢትዮጵያ

ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ
አስተዳደራዊ ክልሎች - ትግራይ | አፋር | አማራ | ኦሮሚያ | ሶማሌ | ቤንሻንጉል-ጉምዝ | ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች | ጋምቤላ | ሐረሪ | አዲስ አበባ | ድሬዳዋ
ቋንቋዎች - አማርኛ | ግዕዝ | ኦሮምኛ | ትግርኛ | ጉራጊኛ | ሶማሊኛ | አፋርኛ | ሲዳምኛ | ሃዲያኛ | ከምባትኛ | ወላይትኛ | ጋሞኛ | ከፋኛ | ሃመርኛ | ስልጢኛ | ሀደሪኛ
መልክዓ-ምድር - አባይ | አዋሽ | ራስ-ዳሽን | ሶፍ-ዑመር | ጣና | ደንከል | ላንጋኖ | አቢያታ | ሻላ
ከተሞች - የኢትዮጵያ ከተሞች