ሚካኤል (ቅዱስ ሚካኤል) በክርስትና እምነት ከሶስቱ ዋና መላእክት (ሚካኤል፡ ገብርኤል፡ ሩፋኤል) አንዱ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰው በተረፈ ዳንኤል ሲሆን በዮሃንስ ራዕይ 12፡7 ላይ በግልጽ ተጠቅሷል። የስሙም ትርጉም «እንደ እግዚአብሄር ያለ ማን አለ?» ማለት ነው።