ደማስቆ

ከWikipedia

ደማስቆ (ወይም ደማስቆስአረብኛ፦ دمشق) የሶርያ ዋና ከተማ ነው።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 2,381,800 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 1,861,900 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 33°30′ ሰሜን ኬክሮስ እና 36°19′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

በአንዳንድ ሊቃውንት ዘንድ፣ ደማስቆ ከሁሉ ይልቅ ረጅሙ እድሜ ያለው ከተማ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ዘንድ በአብርሃም ዘመን ይገኝ ነበር። የሁክሶስ ሕዝብ በ17ኛ ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ በፊት ግብጽን ሲገዙ፣ በአሙሩ ግዛት ውስጥ ነበር። በአማርና ደብዳቤዎች (1350 ክ.በ. ገዳማ) ዲማስቁ ተብሎ በንጉሱ ቢርያዋዛ እንደ ተገዛ ይጻፋል። ከ1100 ክ.በ እስከ 740 ክ.በ ድረስ የአራም ከተማ-አገር ነበር። በዛን ግዜ የአሦር ንጉስ 3 ቴልጌልቴልፌልሶር ያዘው።