የዓለም ዋንጫ

ከWikipedia

የዓለም ዋንጫ በፊፋ (እንግሊዝኛ፦ FIFA) አባል አገሮች የወንድ እግር ኳስ ቡድኖች መካከል የሚከናወን ውድድር ነው። በ1930 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ከ1942 እ.ኤ.አ. እና 1946 እ.ኤ.አ. በስተቀር ውድድሩ በየአራት ዓመቱ ተካሂዷል። የዋንጫና ደረጃ ጨዋታዎቹ በዓለም በብዙ ተመልካቾች ከሚታዩ የስፖርት ዝግጅቶች አንደኛ ነው። የ2002ቱ የዋንጫ ጨዋታ በ1.1 ቢሊዮን ሰዎች እንደታየ ይገመታል።