User talk:Yonas hailemeskel

ከWikipedia

== ዮናስ ሃይለመስቀል የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ስፖርት ሪፖርተር ሲሆን፣ በ1978 ደብረ ሲና በሚባል ቦታ ተወለደ። ከቤተሰቡ ጋር ወደ ጉራጌ ዞን ርእሰ ከተማ ወልቂጤ ተጉዞ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በ ራስ ዘ ስላሴ 1ኛና መ/2ኛ ደ/ት/ቤት ተከታትሏል። የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን በወልቂጤና አዋሳ ከተሞች ከተከታተለ በኋላ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትያትር ጥበባት ትምህርት ክፍል በመግባት በማዕረግ ተመርቋል። በ1999 አ.ም. በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ከተቀጠረ በኋላ ስለሚወዳቸው የሕንድ ፊልሞች ፕሮግራም የሰራ ሲሆን፣ በስፖርት ክፍል በፍላጎቱ በመግባቱ ደስትኛ መሆኑነ ለበርካታ ጊዜያት አጫውቶኛል። የሕንድ ፊልሞችን እንዲሁም የከበደ ሚካኤልን ስነ ጽሁፋዊ ስራዎች በእጅጉ የሚወድ ሲሆን፣ በርካታ ኪነጥበባዊ ጽሁፎችን በተለያዩ መጽሃፍት በቅርቡ ለማሳተም በዝግጅት ላይ ይገኛል። ከነዚህ ምጽሃፍት መሃል፣ የጥበብ ጉባኤ አንዱ ሲሆን፣ በውስጡ አጫጭር ልብ ወለዶችን፣ ግጥሞችን፣ ባለ አንድ ገቢር ተውኔትና ኮሜዲ ቲቨ ሲሪያል ያካተተ መጽሃፍ ነው። ስፖርት ከመውደዱም በላይ፣ የስፖርት ጋዜጠኞችን ይወድ የነበረ ሲሆን፣ ከሚወደውና ከሚያደንቀው ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ከፍቅር ይልቃል ጋር በመስራቱ እራሱን "እድለኛ" ብሏል።




አዘጋጅ፡

ቢንያም ሃይለመስቀል